top of page

ሰበካ ጉባዔ

የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል አጥቢያ ድህረ ገጽን ስለጎበኙ እናመሰግናለን። በካቴድራሉ እምነት፣ ፍቅር እና ኅብረት በአላማ የቆሙበት እንዲሁም ንቁ እና እንግዳ ተቀባይ ማህበረሰብ ያለበት ነው። የሰበካው አባላት ኦርቶዶክሳዊ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችንን ጠብቆ ለማስጠበቅ በተሰጠን አገልግሎት የጊዜ አስራት በማውጣት ለአገልግሎት ቆመናል። ለአካባቢው አዲስ ከሆኑ ወይም በከተማው የኢት/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን አጥቢያ የሚሳተፉበትን መንገዶች እየፈለጉ ከሆነ እንኳን ደህና መጡ! ባለን አቅም በመንፈሳዊ አገልግሎት ልናገለግልዎ ዝግጁ ነን።

በደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል የኢት/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን የሰበካ ጉባዔ አባላት ለሦስት ዓመታት ያገለግላሉ። ከምዕመናን 3 አዲስ የሰበካ ተመራጮች በድምፅ አሰጣጥ ሂደት በቤተክርስቲያኑ ጠቅላላ ጉባኤ ይመረጣሉ። ከካህናት 2 አዲስ የሰበካ ተመራጮች በድምፅ አሰጣጥ ሂደት በቤተክርስቲያኑ ካህናት ጉባኤ ይመረጣሉ። ከሰንበት ትምህርት ቤት 1 አዲስ የሰበካ ተመራጭ በድምፅ አሰጣጥ ሂደት በቤተክርስቲያኑ የሰንበት ትምህርት ቤት ይመረጣል። በእምነት ለማደግ እና ለማገልገል ፣ የቤተ ክርስቲያኑን ተልእኮ ለማስፈጸም በአባልነት ይቀላቀሉ። 

የሰበካ ጉባዔ አባላት

qq_edited.jpg

Melake Bisrat Abba Admasie

Parish Admin

qq_edited.jpg

Mrs. Meskerem Arga

Treasurer

qq.jpg

Liqe Diyakon

Yared Dagnew

Parish Secretary

qq_edited.jpg

Mr. Haile 

Parish Sunday School Rep

qq.jpg

Megabe Sirat

Kesis Assefa Desta

Parish Clergy Rep

qq.jpg

Mr. Eyob Demsie

Accounts Manager

qq_edited.jpg

Mr. Hailemaryam Wolde

Parish Director

bottom of page