top of page

​ሰንበት ትምህርት ቤት

የካቴድራሉ ፈለገ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ሕጻናትና ወጣቶችን ቆየት ያሉ እና በቅርብ የወጡ የመዝሙር ድርሰቶችን እንዲሁም ያሬዳዊ መዝሙሮችን በማሰልጠን የአምልኮ እና የምሥጋና መዝሙር በማቅረብ የሚያገለግል ጠንካራ የቤተ ክርስቲያኑ አካል ነው። በሰንበት ትምህርት ቤቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮን መሠረት ያደረጉ የሃይማኖት ትምህርቶች ፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች፣ ተጨባጭ የህይወት ትምህርቶች የሚሰጥበት እና መንፈሳዊ የኪነ ጥበብ ክህሎት ማሳያ መድረኮች የሚዘጋጁበት ጠንካራ ክፍል ነው። አገልግሎቱ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የሚሰጥ ሲሆን ይህም ታዳጊዎች እና ወጣቶች የማህበረሰቡ አባልነታቸውን እንዲያሳድጉ እና ማንነታቸውን እንዲያጠናክሩ በመንፈሳዊ ህይወታቸው ጠንካራ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባላት እንዲሆኑ ያግዛል።

bottom of page